የአክሱም ዮኒቨርሲቲ የተማሪዎች ዉይይት ተጀመረ

በትምህርት ሚኒስተር ለከፍተኛ ትምህርት ዘርፍ ተማሪዎች በተዘጋጀዉ  የዉይይት መርሃ ግብር መሰረት የአክሱም ዩኒቨርስቲ ተማሪዎች ዉይይታቸዉን ዛሬ ጀምረዋል፡፡ ተማሪዎች በዉጤታማ ትግበራ አሰራር ስርዓት (Deliverology)ፅንስ ሃሳብ ፣ የስነ – ዜጋና ስነ ምግባር ትምህርት ሥኬቶች ክፍተቶችና ቀጣይ አቅጣጫዎች በሚሉና በሌሎች ርእሰ ጉዳዮች ዙርያ ከዛሬ 25 /01/2010 – 27/01/210 ዓ/ም ድረስ ይወያያሉ ፡፡ በዉይይት በአክሱም ዮኒቨርሲቲ በሶስቱም ካምፓሶች የሚገኙ ከሁለኛ ዓመት በላይ የሆኑ ከ7 ሺህ በላይ ተማሪዎች በመሳተፍ ላይ መሆናቸዉ ለማወቅ ተችሏል ፡፡

 

Written by