የአካባቢ ተፅእኖ ጥናት ቀረበ በአገሪቱ

የተለያዩ አከባቢዎች የሚካሄዱ የልማት ስራዎች ቅድሚያ የአካባቢ ተፅእኖ ጥናት (Environmental Impact Assesment) ሊካሄድባቸው እንደሚገባ አንድ ጥናት አመለከተ፡፡ ጥናቱን ያቀረቡት በአክሱም ዩኒቨርሲቲ የሽሬ ግብርና ኮሌጅ የአፋር ሃብትና ተፋሰስ ትምህርት ክፍል መምህር የሆኑት ዶ/ር መኮነን አረጋይ ባቀረቡት ጥናት ልማትና የአካባቢ ተፅእኖ ለማቀናጀት መንግስት አዋጅና ደንብ አውጥቶ እየተንቀሳቀሰ ቢሆንም በአተገባበሩ ላይ ግን ችግር እንዳለበት አመለክተዋል፡፡ ጥናቱ በክልስ ሃሳብና በተግባር ተደግፎ የተሰጠ ሲሆን የአካባቢ ተፅእኖ ገፅታዎች ለመመልከት በአድዋ የአልመዳ ጨርቃጨርቅ ፋብሪካና የሳባ እምነበረድ ፋብሪካ የመልክ ጉብኝት ተካሂዷል፡፡

Written by